Healthcare workers preparing for second strike
Updates
00
D
:
00
H
:
00
M
:
00
S
የተከበራችሁ ውድ የኢትዮጵያ ጤና ባለሞያዎች በሙሉ...እኛ ይህን የጤና ባለሞያውን የዳቦ የህልውና ጥያቄ እየመራን የምንገኝ ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የተውጣጣን ጤና ባለሞያዎች ወደዚህ እንቅስቃሴ ስንገባ ሊደርሱብን የሚችሉ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ነቅሰን በማውጣትና እነዚህንም ችግሮች ለሙያችን ክብር እና ለህልውና ጥያቄያችን ስንል ሙሉ ለሙሉ ለመቀበል አምነን የጀመርነው ሰላማዊ ትግል ነው❗️

የተከበራችሁ ውድ የኢትዮጵያ ጤና ባለሞያዎች በሙሉ...እኛ ይህን የጤና ባለሞያውን የዳቦ የህልውና ጥያቄ እየመራን የምንገኝ ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የተውጣጣን ጤና ባለሞያዎች ወደዚህ እንቅስቃሴ ስንገባ ሊደርሱብን የሚችሉ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ነቅሰን በማውጣትና እነዚህንም ችግሮች ለሙያችን ክብር እና ለህልውና ጥያቄያችን ስንል ሙሉ ለሙሉ ለመቀበል አምነን የጀመርነው ሰላማዊ ትግል ነው❗️

May 14, 2025
የተከበራችሁ ውድ የኢትዮጵያ ጤና ባለሞያዎች በሙሉ
እኛ ይህን የጤና ባለሞያውን የዳቦ የህልውና ጥያቄ እየመራን የምንገኝ ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የተውጣጣን ጤና ባለሞያዎች ወደዚህ እንቅስቃሴ ስንገባ ሊደርሱብን የሚችሉ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ነቅሰን በማውጣትና እነዚህንም ችግሮች ለሙያችን ክብር እና ለህልውና ጥያቄያችን ስንል ሙሉ ለሙሉ ለመቀበል አምነን የጀመርነው ሰላማዊ ትግል ነው❗️
ይህን ስንጀምርም በሀገራችን ያለውን ጥያቄዎችን የማደባበስና ለመስማት ዝግጁ አለመሆንን በሚገባ ተረድተንና በማህበራዊ ሚዲያ ጩኸት ብቻ በመቅፅበት ለውጥ እንደማይመጣ ጠንቅቀን በማወቅና አስፈላጊ የሆነውን ማንኛውም መስዕዋትነት ከፍለን ሙያችንን ነፃ ለማውጣትና ከአስከፊ የድህነት ኑሮ እንድንላቀቅ ነው።
ስለዚህም በዚህ የሰላማዊ ትግል ሂደት በመንግስት መበርገግና ስልጣንና ሀይልን እንደ አማራጭ በመውሰድ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የስም ማጥፋት፣ ደሞዝ መቀጣት፣ ከስራ መባረር፣ ማስፈራሪያ እና ዛቻ፣ ከሀላፊነት መነሳት፣ ድብደባ፣ እስር ብሎም እስከ ሞት ያሉ መስዋዕትነቶች ሊኖሩ ይችላሉ።
ነገር ግን ልብ በሉ ነገ የኛ ፀሀይ ትወጣለች፤ ከጥቂት የመከራና የችግር ቀናት አልያም ወራት በኋላ በአስከፊ የድህነት ደረጃ መኖራችን ያበቃል፤ ሙያችን የሚገባውን ክብር ያገኛል፤ ትውልድ ለት/ት የሚሰጠው ቦታ ይጨምራል፤ ህዝባችን በአዲሱ የጤና ስርዓት ለውጥ ከምንጊዜውም በበለጠ ሁኔታ የተሻለ ተጠቃሚ ይሆናል።
ስለሆነም ያለምንም ማወላወል እና ጊዜያዊ ችግሮችን ለትልቁ የትግላችን ምስል ሲባል እየተቋቋምን ከማዕከል የሚሰጠንን ትዕዛዝ ያለመሸራረፍ እንተግብር።
ማዕከላዊ ቦርዱ ያላሳወቀውንና ያልፈቀደውን ምንም አይነት ስብሰባ እና ውይይት ከመካፈል እንቆጠብ።
እኛ እራሳችንን አሳልፈን ለጋራ ጥቅማችን ስንል ሰጥተናልና በአንድነት ታዘዙን።
Internet የመዝጋት ሙከራ ሊኖር ይችላል። ከተዘጋ በእቅዳችን መሰረት ሙሉ ለሙሉ ስራ ለማቆም የምንገደድ ይሆናል። አፈናን በፍፁም አንታገስም‼️
አንድነታችን ጥንካሬያችን ሀይላችን‼️
የኢትዮጵያ ጤና ባለሞያዎች ንቅናቄ ቦርድ
©️EHPM Board
አዲስ አበባ
ግንቦት 6, 2017 ዓ/ም