Healthcare workers preparing for second strike
Updates
00
D
:
00
H
:
00
M
:
00
S
ከማይታወቁ አካላት በተደጋጋሚ ጥሪዎች እና "አርፋችሁ አትቀመጡም"  ብጤ የጽሑፍ መልዕክቶች እየደረሱኝ ነው።

ከማይታወቁ አካላት በተደጋጋሚ ጥሪዎች እና "አርፋችሁ አትቀመጡም" ብጤ የጽሑፍ መልዕክቶች እየደረሱኝ ነው።

April 26, 2025
በሳሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ስለጤና ባለሙያ ላለኝ ንቁ ተሳትፎ ከአንድም ሁሌቴ በማላውቃቸው ሰዎች አይ ፒ ( IP) አድራሻዬ እንደተበረበረ መላምቶች አሉ።
ይህ ለትውልድ የሚደረግ ትግል ነው።
አድራሻዬን ከፈለጉ የቢሮዬን አድራሻ እና የስራ ቦታዬን ጨምር እልክላቸዋለሁ።
አዎ የእኔን የሙያ ፈቃድ ከፈለጉ፣ በፍሬም አስጊጨ በክብር እሰጣቸዋለሁ። ከዝህ የከፋ ምንም መጥፎ ነገር አይመጣምና።
በዶ/ር ሀብታሙ ጉዳይ በአብሮነት በመቆም ምን ያህል ጠንካራ እንደሆንን ማሳየት አለብን።
እዚህ ምንም ፖለቲካ የለም እኛ የሳይንስ ሰዎች ነን። ድሆቹ አዎ እኛ ለህልውናችን አንድ ጊዜ ለመደመጥ ዘንዳ የምንጮህ ድምጽ አልባቹ ነን።
የድሬዳዋ ጤና ብሮ ፣ እኛ ካርድ አልባ ህብረት እንዳልሆንን ማወቅ አለበት። የሚንጎትታቸው ብዙ ካርዶች አሉን።
አንድ ሳምንት ስቴቶስኮፓችን መስቀል ከበቂ በላይ ነው።
ለረጅም ጊዜ ከወደ ምስራቅ ኖሬያለሁኝ። ግልጽ ጥያቅያችን ፖለቲካ ማድረጋቸውን ከቀጠሉ ስለ ሳቢያን ሆስፒታል ብዙ ሚስጥራዊ መረጃዎች አሉን ። የቅርብ ጊዜ ባለስልጣናት በሆስፒታሉ በቀድሞ መልካም ስም ላይ ጥቁር ጠባሳወችን አስቀምጠዋል። አለን!
በአሁኑ ጊዜ፣ የጤና ባለሙያዎች ከሀገር ለቀው ሲወጡ ወይም ምንም ዕድል የሌላቸው ሙያቸውን በመተው ወደቤት ስመለሱ ማየት የተለመደ ሆኗል።
strike ብቻ ሳይሆን ለጤና ባለሙያዎች የተሻለ የወደፊት ሁኔታን በሚያመጣ በማንኛውም ችግር ውስጥ በግንባር ቀደም ለመሆን አለሁ። አዎ ማንኛውም እርምጃ!
ያልተቋረጠ አገልግሎት እየሰጡ ሁለተኛ ዜጋ መሆን በጣም ያሳዝናል። ይህ ዕድል በፍፁም መባከን የለበትም!!!
ተጽዕኖ ፈጣሪ ሆነን እንኑር; ተጽኖ ፈጣሪ ሆነን እንሙት!
Via ዶ/ር በረከት አማኑኤል MD ደራሲ
IYE [Influential YouthEthiopia] መስራች እና ስራ አስኪያጅ,